
"Sora" የተሰኘው የOpenai ቪዲዮ መተግበሪያ ተዘጋ
ኦፕን ኤአይ (OpenAI) "Sora" የተሰኘው ተወዳጅ የቪድዮ መተግበሪያ ለጊዜው አገልግሎት ማቆሙን አስታወቀ።
ምንም እንኳን ቴክኖሎጂው ከፍተኛ ዝና ቢያተርፍም የሚጠይቀው በቀን እስከ 15 ሚሊዮን ዶላር ወጪ ከሚያስገኘው ገቢ በላይ መሆኑ በጊዝያዊነት ለመዝጋት መገደዱን አሳውቋል።
ይሁንና OpenAI የቪዲዮ ቴክኖሎጂውን "Spud" በሚል የኮድ ስም ወደሚጠራው የቀጣይ ትውልድ ሞዴሉ እያዛወረው እንደሆነ ሲጨርስ መልሶ ወደ አገልግሎት እንደሚያስገባው ገልጿል።
ይህ አዲሱ ሞዴል ትኩረቱን በቫይራል ቪዲዮዎች ላይ ሳይሆን በተቋማት ምርታማነት እና በተለያዩ ዘርፎች (multimodal) የማመዛዘን ብቃት እንዲኖረው የሚያደርግ ይሆናል።
ዘገባዎች እንደሚያመለክቱት OpenAI ትኩረቱን ከመገናኛ ብዙሃን መሳሪያነት ወደ ወኪል AI (Agentic Reasoning) የሚያስቀይረው ከመሆኑም በላይ አሁን ያለውን ወጪ በከፍተኛ ደረጃ መቀነስ እንደሚያስችለው ታውቋል።
አዲሱ "Spud" የተሰኘ የቀጣይ ትውልድ ሞዴል በቴክኖሎጂው ማህበረሰብ ውስጥ ለGPT-5 ተተኪ ሞዴል የተሰጠ የኮድ ስም እንደሆነ ይታመናል።
Comments (0)
Sign in to Comment
You need to be signed in to leave a comment.
You Might Also Like

አፕል የመጀመሪያውን ተጣጣፊ አይፎን በ2026 ሊያስተዋውቅ ነው
አፕል ለዓመታት ሲጠበቅ የነበረውን የመጀመሪያውን ተጣጣፊ አይፎን በመጪው መስከረም 2026 ለገበያ ለማቅረብ ዝግጅቱን አጠናቋል። ይህም ለመላው ዓለም የአፕል ደንበኞቹ ትልቅ የምስራች ሆኗል።

"Sora" የተሰኘው የOpenai ቪዲዮ መተግበሪያ ተዘጋ
OpenAI በቀን $15 ሚሊዮን የሚፈጀውን Sora መተግበሪያ ዘጋ፤ የቪዲዮ ቴክኖሎጂውን ወደ “Spud” ለማዛወር እየሰራ ነው። ትኩረቱም ከቫይራል ቪዲዮ ይልቅ ለድርጅቶች ምርታማነትና ለወኪል AI (Agentic AI) ይሆናል።
